የብዝሀ ሕይወት ማዕከል ወደ ሆነችው ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጡ!

የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት አመሰራረት

የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት እ.ኤ.አ ግንቦት 1976 በኢትዮጵያና በጀርመን መንግስት መካከል በተደረገው የትብብር ስምምነት መሠረት የእጽዋት ጀነቲክ ሀብት ማዕከል (A Plant Genetics Resource Center) በሚል ለመጀመሪያ ጊዜ ተቋቋመ፡፡ ዋና ዓላማውም የሀገሪቱን የዕጽዋት ሀብቶች ከሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች መጠበቅና የሰብል ምርቶችን ለማሻሻል ነበር፡፡ ቀጥሎም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. አፕሪል 5/1994 54ኛዋ ሀገር ሆና የዓለም አቀፍ የብዝሀ ሕይወት ስምምነት ስትፈርም ይህንን ለማስፈፀም ይቻል ዘንድ በእጽዋት ላይ ብቻ ሲሰራ የቆየውን የእጽዋት ጀነቲክ ሀብት ማዕከል (PGRC/E) የእንስሳትና የደቂቅ አካላት እንዲጨምር ተደርጎ ሕይወታዊ ሀብት ጥበቃና ምርምር ኢንስቲትዩት (EBIR) በሚል በአዲስ መልክ ተመሰረተ፡፡ እ.ኤ.አ በ2004 በአዲስ መልክ ጥበቃ ላይ እንዲያተኩር ታስቦ የብዝሀ ሕይወት ጥበቃ ኢንስቲትዩት (EBI) በሚል ተቋቋመ፡፡ በመጨረሻም አሁን የያዘውን ቅርጽ በመያዝ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት በሚል እኤአ በ2013 ተቋቋመ፡፡

ኃላፊትነት፣ ስልጣንና ተግባራት

ኢትዮጵያ የብዝሀ ሕይወት ሀብቶችን ለመንከባከብ በብሔራዊ ደረጃ ግልጽ ፖሊሲ ቀርጻለች፡፡ የእጽዋት ጀነቲክ ሀብት ማዕከል (A Plant Genetics Resource Center) በሚል ለእጽዋት ብቻ ትኩረት ሰጥታ ስትሰራ ቆይታለች፡፡ ከ1998 እ.ኤ.አ ጀምሮ በእጽዋት ላይ ብቻ ሲሰራ የቆየውን የእጽዋት ጀነቲክ ሀብት ጥበቃ ለሁሉም ዓይነት ማለትም ለእጽዋት፣ እንስሳትና ደቂቅ አካላት እንዲጨምር ተደርጎ ዘላቂ ተጠቃሚነትና ተያያዥ የማህበረሰብ እውቀቶችን መጠበቅንም አካቷል፡፡ ስርዓተ ምህዳርም የትኩረት ማዕከል እንዲሆን ተደርጓል፡፡ የሀገሪቱን የብዝሀ ሕይወት ሀብቶች በዘላቂነት የመጠበቅና የማስተዋወቅ ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡ ዓለም አቀፍና የሁለትዮሽ ስምምነቶችን በማዳበር የቴክኒክ ድጋፍ ይሰጣል፡፡ አገሪቷ ለተቀበለቻቸው ብዝሀ ሕወትን የሚመለከቱ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ተጠሪ በመሆን ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ይዋዋላል፡፡

ራዕይ

በ2033 ዓ.ም የኢትዮጵያን ሕዝብና ተፈጥሮ የሚያበለጽግ የብዝሀ ሕይወት ኢኮኖሚ እውን ሆኖ ማየት።

ተልዕኮ

የሀገራችን የብዝሀ ሕይወትና ተያያዥ ነባር ዕውቀቶችን በአግባቡ ማጥናት፣ አሳታፊ የጥበቃ ሥርዓትን መፍጠር፣ ማበልጸግ፣ አርክቦትና ጥቅም ተጋሪነትን በማረጋገጥ ሀብቱ በዘላቂነት ለልማት እንዲውል ማመቻቸት።

ዓላማ

የአገሪቱ ብዝሀ ሕይወት ሀብትና ተያያዥ የማህበረሰቦች እዉቀት በአግባቡ መጠበቃቸዉንና በዘላቂነት ጥቅም ላይ መዋላቸዉን እንዲሁም እነዚህን በመጠቀም ከሚገኘዉ ጥቅም አገሪቷና ማህበረሰቦቿ ፍትሀዊና ሚዛናዊ ድርሻ ማግኘታቸዉን ማረጋገጥ ይሆናል።

Message from the Director General

Dear Visitors, Partners, and Fellow Ethiopians,

Ethiopia is recognized as one of the world’s most biodiverse nations.  Our rugged highlands, vast lowlands, and the rift valley lakes hold the genetic codes of the wild relatives of our staple food, and the endemic wildlife that defines our national identity. The Ethiopian Biodiversity Institute bears the profound responsibility of being the steward of these natural assets since its establishment in the 1970s.

We envision beyond conservation. We are tasked with the dynamic challenge of ensuring that Ethiopia’s genetic resources contribute to the prosperity of our people while remaining protected for the future. Our motto is ‘Conservation PLUS’. It is about unlocking the hidden value of our genetic resources to enrich the people and nature of Ethiopia.

One of our focuses is inventory and research for enhanced conservation and sustainable utilization of our genetic resources and associated indigenous knowledges. We cannot protect what we do not know. Our researchers are continuously working to discover, document, and map the incredible diversity of our genetic resources. We will continue to uncover, identify, and understand Ethiopia’s genetic resource potential through the implementation of digital tools.

In terms of conservation and security, the EBI, through its network of in-situ and gene bank facilities, is securing the biological foundation of Ethiopia’s food sovereignty and ecosystem health. In addition to the gene bank facility at the headquarters in Addis Ababa, we are in the final stages of launching a state-of-the-art duplicate gene bank facility in Fiche, North Shewa. Our gene bank facilities have the capability to conserve the genetic resources of plants, animals, and microorganisms. Expansion of safety duplicate gene banks will continue to ensure agricultural resilience to climate change while protecting indigenous genetic heritage. The expansion and strengthening of in-situ conservation mechanisms, such as community seed banks and biosphere reserves, should also receive due attention.

We are also committed to the principles of Access and Benefit Sharing (ABS). We believe that the communities and the nation that preserve our genetic resources must be the primary beneficiaries when they are used for commercial or scientific purposes. The negotiation tables are aligned with national interests and community benefits. Notable recent actions may include, but are not limited to, the collaborations established with Docomo Oils PLC on Osyris quadripartite, CGS Sementi on Eragrostis tef, and Etcare on Spirulina.

There is a real challenge of climate change, habitat loss, and invasive alien species.  We cannot succeed alone. Whether you are a student seeking knowledge, a researcher looking for collaboration, or a citizen wanting to contribute, your engagement is vital.

Dr. Karta K. Kalsa
ዋና ዳይሬክተር
Ethiopian Biodiversity Institute
አዲስ አበባ

ሁነቶች በፎቶ

የኢትዮጵያ ብዝሀ ህይወት ኢንስቲትዩት ከRoyal Botanic Gardens, Kew ከኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ስትራቴጂካዊ ምርምርን ያከናውናል፡፡
የኢትዮጵያ ብዝሀ ህይወት ኢንስቲትዩት ከRoyal Botanic Gardens, Kew ከኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ስትራቴጂካዊ ምርምርን ያከናውናል፡፡
previous arrowprevious arrow
next arrownext arrow

የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት አደረጃጀት

ኢንስቲትዩቱ ሰባት የምርምር መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች ያሉት ሲሆን እነርሱም፡- የእንስሳት ብዝሀ ሕይወት ምርምር መሪ ሥራ አስፈጻሚ፣ የአዝዕርትና ሆርቲካልቸር ብዝሀ ሕይወት ምርምር መሪ ሥራ አስፈጻሚ፣ የደንና ግጦሽ መሬት ዕፅዋት ብዝሀ ሕይወት ምርምር መሪ ሥራ አስፈጻሚ፣ የጀነቲክ ሀብት አርክቦትና ጥቅም ተጋሪነት ምርምር መሪ ሥራ አስፈጻሚ፣ የደቂቅ አካላት ብዝሀ ሕይወት ምርምር መሪ ሥራ አስፈጻሚ፣ የስልጠና፣ ማማከርና ፕሮጀክት ክትትልና ድጋፍ መሪ ሥራ አስፈጻሚ እና የማዕከላትና ዕፅዋት አፀዶች አስተባባሪ ናቸው። በተጨማሪም አስር የአስተዳደር ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚዎች ያሉት ሲሆን፣ እነርሱም፡- የመሠረታዊ አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ፣ የሰው ሀብት አስተዳደርና ብቃት ሥራ አስፈጻሚ፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ሥራ አስፈጻሚ፣ የተቋማዊ ለውጥ ሥራ አስፈጻሚ፣ የግዥና ፋይናንስ ሥራ አስፈጻሚ፣ የስትራቴጅክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ፣ የኦዲት ሥራ አስፈጻሚ፣ የሥነ- ምግባርና የፀረ-ሙስና ሥራ አስፈጻሚ፣ የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ እና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ናቸው፡፡ ኢንስቲትዩቱ 7 (ሰባት) የብዝሀ ሕይወት ማዕከላት መቱ፣ ሀዋሳ፣ ሀረር፣ መቀሌ፣ ጎባ፣ ባህርዳር እና አሶሳ ላይ አሉት፡፡ በተጨማሪም 2 (ሁለት) የዕጽዋት አጸዶች በሻሸመኔ እና ጂማ ሲኖሩት በፍቼ 1 (አንድ) የብዝሀ ሕይወት ጂን ባንክ አለው፡፡ ኢንስቲትዩቱ በዋና ዳይሬክተር እና በም/ዋ/ዳይሬክተር የሚመራ ሲሆን የስራ አመራር ኮሚቴው ሁሉንም ሥራ አስፈጻሚዎች አቅፎ አመራር ይሰጣል፡፡