በኢትዮጵያ ባዮስፌሮች ዙሪያ የምክክር መድረክ ተካሄደ Post author:በፍቃዱ ከፈለኝ Post published:June 21, 2023 Post category:Uncategorized በኢትዮጵያ በሚገኙት ባዮስፌሮች ዙሪያ ማክሰኞ ሰኔ 13 ቀን 2015 ዓ.ም በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡የዬኔስኮ ፕሮግራም ልዩ ባለሙያ ዶ/ር ሳሙኤል ፓርቴይ የምክክር መድረኩን ዓላማና የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ዶ/ር መለሰ ማርዮ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር የመክፈቻ ንግግር አቅርበዋል፡፡የሁሉም ባዮስፌሮች ሪፖርት፣ የሰውና ተፈጥሮ ብሔራዊ ኮሚቴ እንዲሁም የባዮስፌር ሪዘርቭ ኔትዎርክ ሰነዶች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ቀጣይ አቅጣጫዎች ተቀምጠው የዕለቱ የምክክር መድረክ መጠናቀቁ ታውቋል፡፡ ተጨማሪ ዜናዎች በናጎያ ፕሮቶኮል ትግበራ ላይ አዲስ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ August 8, 2017 የመግባቢያ ሰነድ ተፈረመ June 9, 2023 በእንስሳት ብዝሀ ሕይወት ጥበቃና ዘላቂ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ስትራቴጂ እና የድርጊት መርሃ ግብር አውደ ጥናት ተካሄደ April 28, 2021
በእንስሳት ብዝሀ ሕይወት ጥበቃና ዘላቂ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ስትራቴጂ እና የድርጊት መርሃ ግብር አውደ ጥናት ተካሄደ April 28, 2021