ኢትዮጵያ አፍሪካን በመወከል ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር በካናዳ ሞንትሪያል ውይይት ተደረገ፡፡ በውይይቱም ላይ በአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ በብዝሃ ህይወት ላይ ያለውን ተጽእኖን ጨምሮ የብዝሀ ህይወት መመናመን መንስኤዎች ተዳሰዋል፡፡ በቂ መጠን ያለው የሃብት ማሰባሰብ አስፈላጊነት፣ ከ2020 በኋላ ያለውን ዓለም አቀፋዊ የብዝሃ ሕይወት ማዕቀፍ በፍጥነት ማፅደቅ እና ለብዝሀ ሕይወት ስምምነት ተገቢውን ትኩረት መስጠት የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች ነበሩ። ርዕሰ-ጉዳዮቹ ትኩረት ተሰጥቷቸው ተግባራዊ እንዲሆኑ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡
![You are currently viewing Ethiopia participates on CBD](https://ebi.gov.et/wp-content/uploads/2022/12/1-1.jpg)
ኢትዮጵያ በአለማቀፉ የብዝሀ ሕይወት ስምምነት ላይ ተሳተፈች
- Post author:በፍቃዱ ከፈለኝ
- Post published:December 19, 2022
- Post category:Uncategorized