በብሔራዊ ሥነ ምህዳር ፕሮጀክት ዳሰሳ ዙሪያ ውይይት ተካሔደ Post author:ፍሬህይወት ብርሀኑ Post published:ግንቦት 3, 2021 Post category:Uncategorized በብሔራዊ ሥነ ምህዳር ፕሮጀክት ዳሰሳ ዙሪያ ውይይት ተካሔደበብሔራዊ ሥነ ምህዳር ፕሮጀክት ዳሰሳ ዙሪያ ነሐሴ 22 ቀን 2010 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ውይይት ተካሄደ።በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ / ር መለሰ ማሪዮ የሥነ ምህዳር ዳሰሳ ለመረጃ ፈላጊዎች ምላሽ የሚሰጡ ፣ ስህተቶችን የሚቀንሱ፣ የወደፊቱን አቅጣጫዎች በማሳየት ለውሳኔ እንደሚረዳ ጠቅሰዋል።የውይይት መድረኩ ዓላማም በሥነ-ምህዳሮች ዙሪያ እውቀትን በማካፈል ግንዛቤን ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።ከብሔራዊ ሥነ -ምህዳራዊ ዳሰሳ የተገኘው መረጃ በሥነ-ምህዳሮች ዙሪያ፣ ስጋቶችን በመለየት፣ እሴቶችን በመረዳት እና አጠቃላይ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ለመገምገም ይረዳናል ብለዋል።አያይዘውም በሥነ -ምህዳር ሥርዓቶች ምደባ ላይ አስተዋፅኦ በማበርከት ረገድ ምሁራን ሚና እንዳላቸው አስታውሰዋል።በስብሰባው ላይ ገለጻዎች ቀርበው ውይይቶችም ተካሂደዋል።የብሔራዊ ሥነ ምህዳር ዳሰሳ ፕሮጀክት ብሔራዊ ሥነ ምህዳራዊ ግምገማዎችን ለማካሄድ እና የግምገማዎችን ውጤት ለውሳኔ አሰጣጥ እንዲረዳ በአገር ደረጃ የተቋቋመ ፕሮጀክት ነው። ተጨማሪ ዜናዎች ብዝሀ ሕይወትና የስነ-ምህዳር አገልግሎት Biodiversity and Ecosystem Service Network (BES Net) ረቂቅ ሰነድ ቀረበ ጥር 5, 2024 ኢትዮጵያ በአለማቀፉ የብዝሀ ሕይወት ስምምነት ላይ ተሳተፈች ታህሳስ 19, 2022 የህዳር ወር ሳይንሳዊ ሴሚናር ተካሄደ ታህሳስ 10, 2021
ብዝሀ ሕይወትና የስነ-ምህዳር አገልግሎት Biodiversity and Ecosystem Service Network (BES Net) ረቂቅ ሰነድ ቀረበ ጥር 5, 2024