ዓለም አቀፍ የጸረ- ሙስና ቀን በዓል ተከበረ Post author:በፍቃዱ ከፈለኝ Post published:December 19, 2022 Post category:Uncategorized ዓለምአቀፍ የፀረ- ሙስና ቀን በዓል “ሙስናን መታገል በተግባር!” በሚል መሪ ቃል በፓናል ውይይት እና በግቢ ጽዳት በኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ህዳር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ተከበረ፡፡አቶ ልዑልሰገድ አበበ በኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት የስነ ምግባርና ጸረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሙስና ጽንሰ-ሀሳብ፣ በኢትዮጵያ የጸረ-ሙስና ትግል አስቻይ ሁኔታዎችና ተግዳሮቶች እንዲሁም የጸረ-ሙስና ትግል አቅጣጫዎችና የባለድርሻ አካላት ሚናን ያካተተ ሰነድ ለውይይት አቅርበዋል፡፡ተሳታፊዎችም የተለያዩ ገንቢ ሀሳቦችን ያቀረቡ ሲሆን ሁሉም ሙስናን ለመታገል የድርሻውን ለመወጣት ዝግጁነቱን አረጋግጧል፡፡አቶ መኳንንት እያዩ የዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ የውይይት መድረኩን ሲያጠቃልሉ ርዕሰ-ገዳዩን ወደ ራሳችን ወስደን ሁላችንም ሚናችንን ልንወጣ ይገባል የሚል መደምደሚያ አቅርበው የዕለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡ ተጨማሪ ዜናዎች ኢትዮጵያ በአለማቀፉ የብዝሀ ሕይወት ስምምነት ላይ ተሳተፈች December 19, 2022 የአረንጓዴ አሻራ መርሀ-ግብር ተከናወነ July 11, 2023 ወርሀዊ ሳይንሳዊ ሴሚናር ቀረበ October 25, 2021