ዓለም አቀፍ የጸረ- ሙስና ቀን በዓል ተከበረ Post author:በፍቃዱ ከፈለኝ Post published:December 19, 2022 Post category:Uncategorized ዓለምአቀፍ የፀረ- ሙስና ቀን በዓል “ሙስናን መታገል በተግባር!” በሚል መሪ ቃል በፓናል ውይይት እና በግቢ ጽዳት በኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ህዳር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ተከበረ፡፡አቶ ልዑልሰገድ አበበ በኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት የስነ ምግባርና ጸረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሙስና ጽንሰ-ሀሳብ፣ በኢትዮጵያ የጸረ-ሙስና ትግል አስቻይ ሁኔታዎችና ተግዳሮቶች እንዲሁም የጸረ-ሙስና ትግል አቅጣጫዎችና የባለድርሻ አካላት ሚናን ያካተተ ሰነድ ለውይይት አቅርበዋል፡፡ተሳታፊዎችም የተለያዩ ገንቢ ሀሳቦችን ያቀረቡ ሲሆን ሁሉም ሙስናን ለመታገል የድርሻውን ለመወጣት ዝግጁነቱን አረጋግጧል፡፡አቶ መኳንንት እያዩ የዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ የውይይት መድረኩን ሲያጠቃልሉ ርዕሰ-ገዳዩን ወደ ራሳችን ወስደን ሁላችንም ሚናችንን ልንወጣ ይገባል የሚል መደምደሚያ አቅርበው የዕለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡ ተጨማሪ ዜናዎች የሰው እና የባዮስፌር ሪዘርቭ ብሔራዊ ኮሚቴ ዓመታዊ ስብሰባ ተካሔደ April 19, 2021 የታብሌት አፕሊኬሽኖች ተዘጋጅተው ለአገልግሎት በቁ October 25, 2021 ኢጋድ የክልሉን ብዝሃ ሕይወት ፕሮቶኮልና ተያያዥ ስትራቴጂዎች በስራ ላይ አዋለ July 27, 2017