You are currently viewing Planting seeds of wheat accessions selected through participatory research was conducted at the Ginir community seedbank

በአሳታፊ የነባር ዘር ምርምር (Participatory Variety Selection) የተገኙ ነባር የስንዴ ዓይነቴዎች (farmers varieties) በምርምር ጣቢያ የመዝራት መርሀ-ግብር ተከናወነ

የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት በSeeds for Resilience Project ድጋፍ በጊኒር ወረዳ ሐረዋ 1 ቀበሌ በሚገኘው የማሕበረሰብ ዘር ባንክ ውስጥ ላለፉት ሦስት ዓመታት ባካሄደው አርሶ አደርን ያሳተፈ የስንዴ ምርምር ሥራ አማካኝነት የተመረጡ አራት ነባር የስንዴ ዓይነቴዎች (farmers varieties) የመዝራት መርሀ-ግብር አከናወነ፡፡ በጊኒር ማህበረሰብ ዘር ባንክ ቅጥር ግቢ ውስጥ በተዘጋጀው ከሁለት ሄክታር በሚበልጥ ማሳ ላይ አስፈላጊውን የመስክ ቅየሳ /Field layout/ በማካሄድ በምርምር የተገኙ አራት ነባር የስንዴ ዓይነቴዎች የመዝራት መርሀ-ግብር የተከናወነ ሲሆን፣ በመርሀ-ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ተመራማሪዎች፣ የጎባ ብዝሀ ሕይወት ማዕከል ተመራማሪዎች፣ የጊኒር ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት የአዝርዕት ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ፣ የጊኒር ማሕበረሰብ ዘር ባንክ አባላትና የአካባቢው አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል፡፡ በምርምር ጣቢያው ለአካባቢው ሥነ-ምህዳር ተስማሚ የሆኑ፣ በሽታን መቋቋም የሚችሉ (rust disease) ፣ የምርት መጠናቸው ከፍተኛ የሆኑ አራት ነባር የስንዴ ዓይነቴዎች (farmers varieties) በSeeds for Resilience Project ድጋፍ በተከናወነው አሳታፊ የነባር ስንዴ ምርምር (Participatory Variety Selection) ማግኘት መቻሉ ይታወቃል፡፡