You are currently viewing Seminar Held

ሴሚናር ተካሄደ

በኢትዮጵያ ብዝሀ ህይወት ኢንስቲትዩት የስልጠና፣ ማማከር፣ ፕሮጀክት ክትትልና ድጋፍ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አስተባባሪነት ዓርብ ነሀሴ 02 ቀን 2017 ዓ.ም በኢንስቲትዩቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ሴሚናር ተካሄደ፡፡

ዶ/ር ሳምሶን ሺመልስ የስልጠና፣ ማማከር፣ ፕሮጀክት ክትትልና ድጋፍ መሪ ሥራ አስፈጻሚ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው ፕሮግራሙን አስተዋውቀዋል፡፡ “Fear and Beer: Linking Bird Behavior, Citizen Science, and Ecology of Hop Plantations” በሚል ርዕስ በProf. dr hab. Piotr Tryjanowski ከ Faculty of Veterinary Medicine Department of Zoology Poznan University of Life Sciences የቀረበ ሲሆን “Symphony of the River Floodplain: Understanding the diversity of waterfowl in the seasonally flooded valley of the Biebrza National Park” በሚል ርዕስ በ Prof. Dr hab. Łukasz Jankowiak ከ Institute of Biology, University of Szczecin ገለጻ ቀርቧል፡

በቀረቡት ገለጻዎች ላይ ከተመራማሪዎች የተለያዩ ጥያቄዎች ቀርበው ምላሾች ተሰጥተውባቸዋል፡፡ በሴሚናሩ ማጠቃለያ ላይ ዶ/ር ተስፉ ፈከንሳ በኢትዮጵያ ብዝሀ ህይወት ኢንስቲትዩት የእንስሳት ምርምር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ለገለጻ አቅራቢዎቹ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በቀጣይም በኢትዮጵያና በፖላንድ መካከል በትብብር የሚከናወኑ ተግባራት ሊጠናከሩ እንደሚገባ ሀሳብ አቅርበው ሴሚናሩ ተጠናቋል፡፡