You are currently viewing The Ethiopian Biodiversity Institute has carried out an indigenous seedling planting program with stakeholders

የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የሀገር በቀል ችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር አከናወነ

የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ማመዴ ቀበሌ በቀዳማዊት ክብርት ዶ/ር ዝናሽ ታያቸው ጽ/ቤት በተገነባው የረገ ኤያት 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ሰኞ ሀምሌ 17 ቀን 2015 ዓ.ም የሀገር በቀል ችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር አከናወነ፡፡

በመርሀ-ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተወካዮች፣ የጉራጌ ዞን አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ሰራተኞች፣ የአበሽጌ ወረዳ አመራሮች፣ የክረምት በጎ አድራጎት ፍቃደኞችና የአካባቢው ነዋሪዎች በተገኙበት ተከናውኗል፡፡

መርሀ-ግብሩን በተመለከተ የተለያዩ መልዕክቶች በዶ/ር መለሰ ማርዮ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር፣ ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር፣ ዶ/ር ዮሀንስ ገብሩ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዘዳንት፣ አቶ ምህረት ወንባርጋ የጉራጌ ዞን አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ እንዲሁም አቶ ዘመተ አይፎክሩ የአበሽጌ ወረዳ ም/አስተዳዳሪ እና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ ተላልፈዋል፡፡

በት/ቤቱ ቅጥር ግቢ ጉብኝት የተካሂደ ሲሆን በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት መርሀ-ግብሩ ተጠናቋል፡፡