የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ከቻይና የሳይንስ አካዳሚ ልዑካን ቡድን አባላት ጋር ማክሰኞ ጥር 14 ቀን 2016 ዓ.ም በኢንስቲትዩቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አደረገ፡፡ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መለሰ ማርዮ ለልዑካን ቡድኑ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው ስለ ኢንስቲትዩቱ አጠቃላይ መረጃዎችና የሚያከናውናቸውን ተግባራት በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
ፕሮፌሰር Yunting Fang የ Institute of Applied Ecology (IAE) ም/ዋና ዳይሬክተር በበኩላቸው ስለ ኢንስቲትዩታቸው ገለጻ አቅርበው ውይይት ተደርጓል፡፡ በውይይቱ ወቅት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር ቻይና እና ኢትዮጵያ የሚያመሳስላቸው በርካታ ጉዳዮች መኖራቸውን አስታውሰው በትብብር የምንሰራቸው በርካታ ርዕሰ-ጉዳዮች አሉ ብለዋል፡፡
በሁለቱም ተቋማት መካከል በጋራ መስራት የሚቻልባቸውን ጉዳዮች በመለየት የመግባቢያ ሰነድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ ለመግባት ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
