በኢትዮጵያ ባዮስፌሮች ዙሪያ የምክክር መድረክ ተካሄደ Post author:በፍቃዱ ከፈለኝ Post published:June 21, 2023 Post category:Uncategorized በኢትዮጵያ በሚገኙት ባዮስፌሮች ዙሪያ ማክሰኞ ሰኔ 13 ቀን 2015 ዓ.ም በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡የዬኔስኮ ፕሮግራም ልዩ ባለሙያ ዶ/ር ሳሙኤል ፓርቴይ የምክክር መድረኩን ዓላማና የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ዶ/ር መለሰ ማርዮ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር የመክፈቻ ንግግር አቅርበዋል፡፡የሁሉም ባዮስፌሮች ሪፖርት፣ የሰውና ተፈጥሮ ብሔራዊ ኮሚቴ እንዲሁም የባዮስፌር ሪዘርቭ ኔትዎርክ ሰነዶች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ቀጣይ አቅጣጫዎች ተቀምጠው የዕለቱ የምክክር መድረክ መጠናቀቁ ታውቋል፡፡ ተጨማሪ ዜናዎች የደቂቅ አካላት ቴክኖሎጂ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል May 28, 2018 በብሔራዊ ሥነ ምህዳራዊ ግምገማ ምዘና ላይ አውደ ጥናት ተካሄደ February 28, 2018 የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የሀገር በቀል ችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር አከናወነ July 25, 2023